top of page

የጎንደር ሕብረት (ጎሕ) አላማው ምንድን ነው?

  • የክፍለሀገሩን ተወላጆች ያሰባሰበ፤ ለህዝቡ ደህንነትና ታሪካዊ አንድነት ጠበቃ ሆኖ የሚከራከር

  • በአጠቃላይ በኢትዮጵያ እና በተለይ በጎንደር ክፍለሀገር፤  የሰፈነው የዘር 
    ሥርዓት ተወግዶ፣ ፓለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፍትህ እንዲሰፍን አጋር ሆኖ የሚታገል ድርጅት ነው።

 

የጎንደር ሕብረት ተግባር ምንን ያካትታል? 

  • በመላው አለም የሚገኙ የጎንደር ክፍለሀገር ተወላጆችን ማደራጀት።

  • የድርጅቱ ልሳን የሚሆን መፅሄት ማዘጋጀት።

  • የሚሰራውን ግፍ የውጭ ሰባአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች እንዲያውቁት 
    ማድረግ።

  • በዓለም ደረጃ ዘረኛውንና ተስፋፊውን መንግስት ምንነት/ማንነት ማጋለጥ።

  • የፕሮፖጋንዳ ስራዎችን ማካሄድ። 

  • የመረጃ ማሰባሰብ ስራዎችን ማከናወን።

  • በአጠቃላይ በሀገራችን በተለይ በክፍለሀገራችን ለፍትህ የሚደረገውን ትግል
     ድጋፍ መስጠት።

  • የተፈጠሩ ችግሮችን ለመፍታት ለሽምግልና የሚሆኑ ሰዎችን ማግኘትና ጥረት 
    ማድረግ።

  • የድርጅቱ ዘላቂ፣ አሰራር እና አወቃቀር በሂደት ማሻሻል።

bottom of page