ጎንደር የጦር አውድማ፤ የነጻነት ማማ!
የጎንደር ሕብረት መሥራቾች፤ ጎንደር መነሻችን፤ ኢትዮጵያ መዳረሻችን ብለን የተነሳነው፤ የታሪክን ሃቅ መሰረት አድርገን ነው። አብነታችን፤ ከድሮ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ኢትዮጵያን ለማጥቃት የተነሱ ጠላቶቻችን፤ የጥቃት ጦራቸውን የሚያዘምቱት በጎንደር በኩል መሆኑ ነው። ከብዙ ጥቂቶቹን ደጋግመን ማንሳት እንደሞከርነው፤ የሩቅ ጠላቶቻችን በተደጋጋሚ የግንባር ወረራቸውፍን በተግባር ለመፈፀም የሚሞክሩት፤ የጎረቤት አገር የሆነችውን፤ ሱዳንን በመጠቀም በጎንደር በኩል አድርገው ነው።