Central Gondar Communication
November 13 at 2:25 AM ·
የጎንደር ህብረት ለኢትዮጵያ አንድነት የግማሽ ሚሊዮን ብር የመጀመሪያ ዙር ድጋፍ አደረገ
ጥቅምት 04/2013 የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ
የጎንደር ህብረት ለኢትዮጵያ አንድነት የግማሽ ሚሊዮን ብር የመጀመሪያ ዙር ድጋፍ አደረገ
የጎንደር ህብረት ለኢትዮጵያ አንድነት ማህበር ለጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ለአማራ ልዩ ሀይልና ለሚሊሻ አባላት የግማሽ ሚሊዮን ብር የመጀመሪያ ዙር ድጋፍ ማድረጋቸውን የማህበሩ ተወካይ የሆኑት አቶ አምላኩ ነጋሽ ተናግረዋል፡፡
አቶ አምላኩ ነጋሽ አክለውም ድጋፉ የተሰበሰበው አሜሪካን አገር ከሚኖሩ የጎንደር አካባቢ ተወላጆች ሲሆን መንግስት የጀመረውን ህግ የማስከበር ስራ እንደሚደግፉና በቀጣይም ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል፡፡
የጎንደር ቀጠና ሎጅስቲክ አስተባባሪ የሆኑት አቶ ባንቲሁን መኮነን በበኩላቸው አሁን ላይ በየደረጃው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በርካታ ድጋፎችን እያደረጉ እንደሚገኙ ገልፀው በዛሬው እለትም የጎንደር ህብረት ለኢትዮጵያ አንድነት ማህበር የ500 ሽ ብር ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡
አቶ ባንቲሁን አክለውም የጎንደር ህብረት ማህበር ከዚህ በፊት አካባቢው ላይ ተፈጥረው በነበሩ ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ምክንያቶች ማህበሩ በርካታ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰው አሁን ላይም ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ ከአማራ ልዩ ሀይልና የሚሊሻ አባላት ጎን መሆናቸውን አሳይተዋል ብለዋል፡
Central Gondar Communication
10h ·
በሰሜን አሜሪካና ጀርመን ሀገር ከሚኖሩ የጎንደር ህብረት ለኢትዮጵያ አንድነት እንዲሁም የጎንደር ልማት ማህበር የአንድ መቶ ኩንታል በቆሎ ድጋፍ አደረጉ።
ጥቅምት 12/2013 የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ
በሰሜን አሜሪካና ጀርመን ሀገር ከሚኖሩ የጎንደር ህብረት ለኢትዮጵያ አንድነት እንዲሁም የጎንደር ልማት ማህበር የመቶ ኩንታል በቆሎ ድጋፍ ማድረጋቸውን የህብረቱ ተወካይ የሆኑት አቶ አምላኩ ነጋሽ ተናግረዋል።
ድጋፍ የተደረገላቸው በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ ደንቢያ በጎርፍ ለተፈናቀሉ ወገኖች መሆኑን አስረድተዋል።
አቶ አምላኩ ነጋሽ ጨምረው አንደገለፁት ህብረቱ የወገን ደራሽነቱን ያሳየበት ተግባር ሲሆን በዚህ በያዝነው ወር በተመሳሳይ መልኩ ለደቡብ ጎንደር ዞን በጎርፍ ለተፈናቀሉ ወገኖች 176 ኩንታል ድጋፍ ማድረጋቸውን አብራርተዋል።
በርክክብ ስነ-ስርዓቱ የተገኙት የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ተወካይ አቶ እምቢአለ ታረቀኝ በበኩላቸው ለወገን ደራሽ ወገን ነውና የተሰጠውን እርዳታ በተፈናቃዮች ስም ከልብ እያመሰገን ሌሎች ወገኖችም አስፈላጊውን ድጋፍ እንድታደርጉልን ጥሪያችን እናቀርባለን ብለዋል።
የጎንደር ህብረት ከአሁን በፊት በጭልጋና አካባቢው በተፈጠረው ግጭት ለተፈናቃይ ወገኖች ድጋፍ ማድረጋቸውን አቶ እምቢአለ ታረቀኝ አንስተው ድርጅቱ ሁሌም ከጎናች መሆኑን አሳይቶናል ብለዋል።
በዋኘው አዳነ
South Gondar Zone Communication
October 15 at 2:42 PM ·
በደቡብ ጎንደር እስተዳደር ዞን በፎገራ፣ ሊቦ እና ደራ ወረዳወች በጣና ወደኋላ መመለስ መክንያት ጉዳት ለደረሰባቸውን አርሶ አደሮች 176.7 ኩንታል በቆሎ ድጋፍ ተደረገላቸው፡፡
የደቡብ ጎንደር እስተዳደር ዞን አደጋ መከላከልእና ምግብዋስትና ተጠሪ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አገኘሁ ዳኛው በሶስቱ ወረዳወች በ7 ቀበሌወች በጣና ወደኋላ መመለስ ምክንያት ከመኖሪያ አካባቢያቸው ለተፈናቀሉ አርሶ አደሮች ከተለያዩ ረጅ ድርጅቶች፣ማህበራት እና ባለሃብቶች ድጋፍ እየተደረገላቸው እንደሆነ ጠቁመው በእለቱ ከስሜን አሜሪካ እና በጀርመን አገር የሚኖሩ የጎንደር ህብረት እና የጎንደር መልሶ ማቋቋምና ልማት ማህበር አባላት 176.7 ኩንታል በቆሎ ድጋፍ መደረጉን አስመልክቶ በዞኑ ተጎጅ አርሶ አደሮች ስም የላቀ ምስጋና አቅርበዋል ፡፡
አቶ አገኘሁ አክለውም እነዚህን አርሶ አደሮች በዘላቂነት ለማቋቋም ውሃው እየሸሸ ሲሄድ የተለቀቀውን ማሳ በተተኪ ዘር እየሸፈኑ ምርት እንዲያመርቱ አሁን ላይ ሰፊ የሆነ ቅንጅታዊ ስራ የሚጠይቀው ከ 8ሽህ 500 ኩንታል በላይ ተተኪ ዘር በተገቢው መንገድ እንዲቀርብ ማድረግ ነው፡፡ከዚህ ጎን ለጎን እንደ የውሃ ፣ትምህርት፣ ጤና እና መሰል ተቋማት እንዲሟሉ በማድረግ ወደ ቀያቸው የመመለስ ስራ በቅንጀት መስራት እንዳለበት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የደቡብ ጎንደር መልሶ ማቋቋምና ልማት ማህበር ስራ አስኪያጅ አቶ ሞላ እንግዳ በእርክክቡ ላይ ተገኝተው ማህበሩ በስሜን አሜሪካ እና በጀርመን አገር የሚኖሩ የጎንደር ህብረት ማህበር ጋር በመቀናጀት ከዚህ ቀደም የኮሮና ውረርሽኝን ለመከላከል ለ5ቱ ዞኖች 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚገመት ዘይት እና የፊኖ ዱቄት ድጋፍ እንዳደረገ ጠቁመው በእለቱ 176.7 ኩንታል በቆሎ በጎንደር ከተማ የጎንደር ህበረት ኮሚቴ ጸሀፊ ከወጣት ምህረት አምሳሉ እና ሆነልኝ አበበ ጋር አስረክበዋል፡፡
ወጣት ምህረት አምሳሉ እና ሆነልኝ አበበ ማህበሩ ጉዳት ለደረሰባቸው አካባቢወች እለታዊ ድጋፍ የማድረግ ስራ ሲሰራ እንደቆየ ጠቁመው በቀጣይ መሰረቱን ጎንደር ላይ በማድረግ አገር በቀል መንግስታዊ ያለሆነ ተቋም ሁኖ በዞኑ ያሉ ችግሮችን በመለየት ችግር ፈች በሆኑ መሰረተ ልማቶች ላይ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
በእርክክብ ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አወቀ ዘመነ የጎንደር ህብረት በአሜሪካ እና ጀርመን አገር የሚኖሩ ተወላጆች ከዚህ በፊት የኮሮና ወረርሽኝን ለመከላከል ከ300 ሽህ ብር በላይ ወጭ በማድረግ 300 ኩንታል ፊኖ ዱቄት እና 517 ሊትር ዘይት ለችግር ለተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡
እንዲሁም የእርብ እና የጉማራ ወንዞች የክረምት የጎርፍ ውሀ የመሸከም አቅማቸው እንዲያድግ ዞኑና የክልሉ መንግስት በቅንጅት ባደረገው ጥረት ውጤት ያስገኘ እንደሆነ ጠቁመው የጣናን ወደኋላ መመለስ ተከትሎ በደራ ፣ፎገራ እና ሊቦ ከምከም ወረዳዎች ጉዳት የደረሰ በመሆኑ ህብረተሰቡን ለማገዝ በሚደረገው ጥረት ገንዘብ በማሰባሰብ በ220 ሽህ 885 ብር 176.7 ኩንታል ለምግብነት የሚውል በቆሎ በዛሬው እለት አስረክበውናል፡፡ በመሆኑም ድጋፉን ላደረሱት እና ገንዘቡን ለለገሱ ሁሉ በዞኑ ስም የላቀ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የደቡብ ጎንደር አስተዳደር ዞን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጽ/ቤት
ጥቅምት 06/2013 ዓ/ም
ዘጋቢ፣ምህረት አለሙ