top of page

Empower
Growth

የጎንደር ሕብረት ለጎንደር ተፈናቃዮች አንድ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር መደበ

  • Writer: Abebe Gelagay
    Abebe Gelagay
  • Feb 21, 2019
  • 1 min read

የካቲት 13 2011 ዓ. ም.(2/20/2019)

የጎንደር ሕብረት ለጎንደር ተፈናቃዮች አንድ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር መደበ

ባለፉት ወራት በመሃልና በምዕራብ ጎንደር በተፈጠረው ቀውስ ምክንያት በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ነዋሪዎች መፈናቀላቸው ሲዘገብ ሰንብቷል። ቀውሱ በመተማና አካባቢው ሲጀምር መንግሥት ፈጥኖ እርምጃ ባለመውሰዱ ልዩ ልዩ አጀንዳ ያላቸው ታጣቂ ሃይሎች ሁኔታውን በመጠቀም ቀውሱ እንዲባባስ ለማድረግ እድል አግኝተዋል። በዚህም ምክንያት ከመተማ እስከ ጎንደር እና ከጎንደር እስከ ትክል ደንጋይ ከዚያም አልፎ ወደ ሁመራ በሚወስደው መንገድ ሁሉ ችግሩ እንዲባባስ ሆኗል። በዚህም ምክንያት ከ 50000 እስክ 60000 የሚሆኑ ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል። በአሁኑ ወቅት በትክል ደንጋይ፣ በአይምባ፣ በወለቃ፣ በመተማ አካባቢና በሌሎችም አካባቢዎች የሚገኙ ሲሆን፤ ወደ ሱዳን የገቡ ተፈናቃዮችም እንዳሉ ይነገራል።

የጎንደር ሕብረት ጎንደር ባለው ቅርንጫፍ ቢሮው በኩል ሁኔታውን ሲከታተልና እርዳታ ለማድረስ የፀጥታውን አመችነት ሲለካ ቆይቷል። ከዚህ የተላኩ አባሎቹ ትክል ደንጋይ፣ ወለቃ እና አይምባ በመሄድ ተፈናቃዮችን አናግረዋል። ያሉበትን ሁኔታ ተረድተዋል። ሌሎችንም ተፈናቃዮች አሉባቸው የተባሉትን ቦታዎች ለማየትና የችግሩን መጠን ለማወቅ ጥረቱ ቀጥሏል።

የጎንደር ሕብረት በደረሱት ዘገባዎች ላይ ተመስርቶ ለተፈናቃዮች እርዳታ ለማድረስ አንድ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር (1,000,000.00) መድቧል። እርዳታውም በአስቸኳይ እንዲደርስ ጎንደር ላለው ቅርንጫፍ መልእክት ያስተላለፈ ሲሆን፣ መሬት ላይ ባለው ዘገባ ላይ ተመስርቶ እንደሁኔታው የእርዳታውን መጠንም ከፍ ለማደርግ ወስኗል። አባላቱም ሆኑ ደጋፊዎች የወገኖቻችንን ሰቆቃ ለመቀረፍ በሚደረገው ጥረት በስቴት ቅርንጫፎች በኩል ገንዘብ በማሰባሰብ የበኩላቸውን አስተዋጽዎ እንዲያደርጉ ጥሪያችን እናቀርባለን።

የጎንደር ሕብረት ከዚህ በፊት የቤንሻንጉል የወልቃይትና የራያ ወግኖች በተፈናቀሉበት ጊዜ ለነዚህ ወገኖች ፈጥኖ እርዳታ እንዳደረሰ የሚታወስ ነው።

 
 
 

Comments


Featured Posts
Recent Posts
Search By Tags
Follow Us
  • Facebook Classic
  • Twitter Classic
  • Google Classic

WELCOME

Welcome visitors to your site with a short, engaging introduction. Double click to edit and add your own text.

Start Now
david-whipple-mU-wz7JlJMc-unsplash_Ravid.jpg
  • s-facebook
  • Twitter Metallic
  • s-linkedin
bottom of page